Logo
News Photo

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት ምሁራኖቹ የተባባሪ ፕሮፌሰርነት እድገት ሰጠ

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ መማክርት ጉባዔ ኅዳር 13/2017 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ለሁለት የዩኒቨርሲቲው ምሁራን የተባባሪ ፕሮፌሰርነት እድገት አፀደቀ።

የመማክርት ጉባዔው በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሲቪል ምህንድስና እና አርክቴክቸር ኮሌጅ ለዶ/ር ወርቁ ቆሼ ሀረሩ በግንባታ ቴክኖሎጂና ስራ አመራር መስክ እንዲሁም በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ምህንድስና ኮሌጅ ለዶ/ር ግርማ ቤካ ለሙ በኤሌክትሮኒክ ሳይንስና ቴክኖሎጂ መስክ እየሰሩ ያበረከቷቸውን አስተዋፅኦዎች በመገምገም የተባባሪ ፕሮፌሰርነት አካዳሚያዊ የደረጃ እድገት አፅድቋል።

ምሁራኑ ባበረከቷቸው የምርምር፣ የማህበረሰብ አገልግሎት እና የመማር ማስተማር ስራዎች ስኬታማ አፈጻጸማቸው ተገምግመው ከረዳት ፕሮፌሰርነት ወደ ተባባሪ ፕሮፌሰርነት አድገዋል። 

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የተባባሪ ፕሮፌሰርነት አድገት ላገኙት ዶ/ር ወርቁ ቆሼ እና ለዶ/ር ግርማ ቤካ እንዲሁም ተማሪዎቻቸው፣ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ዩንቨርሲቲው እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል።


Dire Dawa University Announces Faculty Promotions

Dire Dawa University is honored to announce the promotion of two esteemed faculty members of Institute of Technology to the distinguished rank of Associate Professor. The promotions were approved by the university Senate on November 22, 2024.

The newly promoted Associate professors are:

1. Dr. Worku Koshe Hareru: Associate Professor of Construction Technology and Management in College of Civil Engineering and Architecture, Dire Dawa University Institute of Technology.

2. Dr. Girma Beka Lemu: Associate Professor of Electronic Science and Technology in College of Electrical and Computer Engineering, Dire Dawa University Institute of Technology.

The university extends its warmest congratulations to these accomplished individuals. Their dedication to research, leadership, teaching, and community service has played a pivotal role in the University's continued success. Their achievements serve as an inspiration to the entire academic community.

Dire Dawa University also recognizes the unwavering support provided by the families, friends, and students of these esteemed Associate Professors. Their encouragement has undoubtedly been instrumental in this well-deserved recognition.

Share This News

Comment