ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮ 2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የመልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ አጠቃላይ ቁጥራቸው 14,780 (አስራ አራት ሺህ ሰባት መቶ ሰማንያ) የማኅበራዊ ሳይንስና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ያለ ምንም ችግር በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም እንዳሳወቁት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የመልቀቂያ ፈተናውን እንዲወስዱ የተመደቡ የማኅበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የፈተናው ሂደት ፍጹም ሰላማዊ እና ስነ-ምግባርን ባከበረ መልኩ ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።
ዶ/ር ኡባህ አያይዘው ዩኒቨርሲቲው ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ያከናወናቸው ተግባራት ፈተናው ያለምንም ችግር በተያዘለት መርሃ-ግብር እንዲከናወን ያስቻለው መሆኑን አሳውቀው ፈተናው በመርሀግብሩ መሰረት ሰላማዊና በተሳካ መንግድ እንዲጠናቀቅ ትልቅ አስተዋፅኦ ለነበራቸው አካለት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
Dire Dawa University is found in the industrial and commercial city of Dire Dawa, which is located at 515 km east of Addis Ababa. It is a young higher education institution, established and started its teaching and learning activities in 2007 academic year.
Copyright © 2021 - 2025 Dire Dawa University. All Rights Reserved.
Share This News