።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከሀረሪ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጋር በመተባበር የወንጀል መዝገብ መረጃ እና አስተዳደር ስርዓት “Crime Record Information and Management System (CRIMS)” የሚል ሶፍትዌርን ለማበልፀግ ስምምነት አድርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ በኢፌዲሪ ፍትህ ሚኒስቴር የወንጀል ሪከርድ መረጃና አስተዳደር ሥርዓት መነሻነት የሀረሪ ክልልን ህጋዊ አሰራርን ለማዘመን የታለመ የለውጥ ስራ ሲሆን በሀገር ደረጃ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስርዓቱን ተከትሎ በተቋሙ አጠቃላይ ዲጂታል ለውጥ እቅድ አካል ነው፡፡ ስርዓቱ በወረዳ ደረጃ ክስ ከመጀመሩ ጀምሮ በዐቃቤ ህግ የወንጀል ክስ እስከመቅረብ ድረስ አጠቃላይ ሂደቱን የሚያቀላጥፍ ሲሆን በወረዳም ሆነ በክልል ያሉ ወንጀሎችን እንደ ዝርፊያ እና አደንዛዥ እፅ ዝውውር ያሉ ጉዳዮችን ጨምሮ የሚቆጣጠር ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ፕሮጀክቱ 1.5 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚደረግበት ሲሆን በስድስት ወራት ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡
Dire Dawa University is found in the industrial and commercial city of Dire Dawa, which is located at 515 km east of Addis Ababa. It is a young higher education institution, established and started its teaching and learning activities in 2007 academic year.
Copyright © 2021 - 2025 Dire Dawa University. All Rights Reserved.
Share This News