የዘንድሮው የሴቶች ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ114ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ49 ጊዜ
"ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል ፡፡
ይህንኑ በማስመልከትም በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በፓናል ውይይት የተከበረ ሲሆን በዚሁ የፓናል ውይይት መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ሃላፊ ዶ/ር ግርማ ቤካ ዩኒቨርሲቲው የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚ የሚያሳድጉ በርካታ ተግባራትን አከናውኗል፡፡
በተለይም ሴት መምህራንን ወደ አመራርነት አንዲመጡ በማድረግና የሴት ተማሪዎች ውጤታማነት ለማሳደግ የተሠሩት ሥራዎች ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡
በፓናል ውይይቱ ላይ የፓለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ካሳሁን ለውይይት መነሻ የሚሆን ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን የማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ዲን የሆኑት ዶ/ር ነፃነት ተከስተ ደግሞ
"ሴቶች የሚገጥማቸውን ጫና ተቋቁመው ስኬታማ መሆን ይችላሉ" በሚል ለፓናሉ ተሳታፊዎች ልምዳቸውን አካፍለዋል፡፡
Dire Dawa University is found in the industrial and commercial city of Dire Dawa, which is located at 515 km east of Addis Ababa. It is a young higher education institution, established and started its teaching and learning activities in 2007 academic year.
Copyright © 2021 - 2025 Dire Dawa University. All Rights Reserved.
Share This News